Saturday 15 September 2018

የመልዕክት ርዕስ ፦ ሁልጊዜ በእግዚአብሔር እንከብራለን ( መዝሙር 43 ( 44 ) ፥ 8የመልዕክት ርዕስ ፦ ሁልጊዜ በእግዚአብሔር እንከብራለን ( መዝሙር 43 ( 44 ) ፥ 8 የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን ከክንፎቹ በታች መጠጊያን አግኝተን በእግዚአብሔር ጥላ ውስጥ የምንኖረው እኛ ክርስቲያኖች ሃይማኖተኞች ሆነን ሃይማኖታችንና ሥርዓታችን ስላስገደደን አይደለም :: ሁልጊዜ በእግዚአብሔር መክበር እንዳለ ስላመንንና ስላወቅን ነው :: የመረጥነው የእምነታችን መንገዱ እምብዛም የማይመች ቢመስለንም እንኳ የመረጠን ጌታ አክባርያችን ነውና ሁልጊዜ በእርሱ እንከብራለ :: ስሙንም ለዘላለም እናመሰግናለን :: ስለዚህ ክርስትና ያታከታችሁ ፣ በሰዎች በሁኔታዎችና በነገሮች ጭምር ተስፋ የቆረጣችሁ ብትኖሩ ዛሬ በእንዲህ ሁኔታ ላላችሁ ለእናንተ መልዕክት አለኝ :: ሁልጊዜ በእግዚአብሔር እንከብራለን ነው የሚለን ቃሉ :: ታድያ አንዳንድ ጊዜ የሚያከብር ሲያሻው ደግሞ እንደፈለገ አድርጎ የሚዘረጥጥ ሰው ነው እንጂ እግዚአብሔር አይደለምና በአምላካችን በእግዚአብሔር ሁልጊዜ እንከብራለን ቅዱሳን በዚህ መልዕክት ተጽናኑ ተባረኩ ሰላም ሁኑ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment