Friday, 2 October 2020

GEDION ASCHALEW "ማንነቴን ሰዋዋለው" Amazing New Ethiopian Gospel Song

#henonstudio #gedi #share ጌታ ይሻልሀል by Gedion Ascha...

 በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በእንተ ሰማንያ አሃዱ (ክፍል-1)
መግቢያ
የቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ምንም እንኳን ኦርቶዶክሳዊው እስቤ መጽሐፍ ቅዱስ ብቸኛው የክርስትና አስተምህሮ መመሪያና ምንጭ ነው ባይልም መጽሐፍ ቅዱስ ለቤተክርስቲያን መተኪያ የሌለው የጽሁፍ ሀብቷ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ብቸኛው የክርስትና አስተምህሮ መመሪያና ምንጭ አይደለም ያልነው ትውፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ ጎን ለጎን አብሮ ስለሚያገለግል ነው። የጽሁፉ ሀሳብ መጽሐፍ ቅዱስን በሚመለከት ስለሆነ ትውፊትን በሚመለከት እራሱን በቻለ ርእስ እንመጣበታለን። መጽሐፍ ቅዱስ ለክርስትና አስተምህሮ መሠረት ነው የሚለው በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት ቢኖረውም በውስጡ ስላሉት የመጽሐፍት ብዛት ግን ልዩነት መኖሩ የታወቀ ነው። በተለይም ፕሮቴስታንታውያን ከሉተር የተሃድሶ እንቅስቃሴ በኃላ እንደ አዲስ የተሰራውን 66ት መጽሐፍት ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሚቀበሉ በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ያሉ (እነርሱ ጋር የሌሉትን) መጽሐፍት ሲተቹ ይታያሉ። ለአብነትም በቴዎድሮስ ደመላሽ "ሰማንያ አሃዱ በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን" የሚለውን መጽሐፍና "ኦርቶዶክስ መልስ ካላት እኛም ጥያቄ አለን" በሚል የተዘጋጀውን ቪሲዲ መጥቀስ ይቻላል። ይህንን መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስላለው በተለምዶ ሰማንያ አሃዱ ስለሚባለው መጽሐፍ ቅዱስ ከስር ከመሠረቱ በመመልከት ለጠያቂዎች ምላሽ አዘጋጅተናል።
=>>>እንደ መንደርደሪያ (አጠቃላይ ጥያቄያዊ መልእክቶች ለፕሮቴስታንታውያን)
1. መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ጊዜና ቦታ የተጻፈ መጽሐፍ እንደሆነ ይታወቃል። በተለይም የሀዲስ ኪዳን መጽሐፍት በተጻፉበት ወቅት ሌሎች ሀሰተኞች መጽሐፍት (ψευδεπγραφα/Peudepigraha) ስለነበሩ እውነተኞችን መጽሐፍት ከሀሰተኞች ለመለየት የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና (Biblical Canonization) መንገድ ተጠቅመዋል። በዚህ የቀኖና ሂደት ውስጥ የተሳተፍት የጥንቷ ቤተክርስቲያን አባቶች (Early Church Fathers) ነበሩ። እነዚህ አባቶች በክህነት የሚያምኑና እራሳቸውም እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ ነበሩ። ይህ ከሆነ ዛሬ ላይ ያሉ በመጽሐፍ ቅዱስ እናምናለን የሚሉ የተለያዩ በክርስትና ስም ያሉ የእምነት ድርጅቶች (ፕሮቴስታንታውያን፣ ጅሆቫ ዊትነስ፣ ኦንሊ ጂሰሶች) የጥንቷ ቤተክርስቲያን አባቶች ሰፍረው እና ለክተው የሰጧቸውን መጽሐፍት ነው የሚጠቀሙት ማለት ነው። እኛም የቤተክርስቲያን አባቶች በምሥጢራተ ቤተክርስቲያን፣ በነገረ ክርስቶስ፣ በምሥጢረ ሥላሴ፣ በነገረ ማርያም፣ በነገረ ድኅነት፣ በነገረ ቤተክርስቲያን ያስተማሩትን ትምህርቶች ለምን አትቀበሉም? ብለን እንጠይቃለን። እውነተኞችን መጽሐፍት ከሀሰተኞች ለይተው ቀንነው በአንድ ጥራዝ የሀይማኖት መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ ከተቀበላቹ ሙሉ ትምህርታቸውን ለምን አትቀበሉም? ለማለት እንወዳለን።
2. ሉተር ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሲወጣ ከጀመራቸው "የብቻ ትምህርቶች" አንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ (Scripture alone) ነው። ይህ አመለካከት ዛሬ ላይ ባሉ የፕሮቴስታንት ዲኖሚኔሽኖችም ዘንድ የሚንጸባረቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ምን ያህል መጽሐፍት እንዳሉት አይዘረዝርም። ጸሀፊያቸው ማን መሆኑን እንኳ የማይናገሩት የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍት ራሳቸውን በራሳቸው አያረጋግጡም። ለምሣሌ የማቴዎስ ወንጌልን እንውሰድ። የማቴዎስ ወንጌል የተጻፈው ከ 12ቱ ሐዋርያት አንዱ በሆነው በማቴዎስ ስለ መሆኑ አንድም ቦታ ላይ እንኳ አይናገርም። እንዲያውም በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ዘመን በማቴዎስ ስም ይሰራጭ የነበረው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ብቻ አልነበረም። ማቴዎስ ወንጌላዊ ጽፎታል ተብሎ ይሰራጭ የነበረ "የተከራካሪው የቶማስ መጽሐፍ- The book of the contender" የሚባል መጽሐፍም ነበር። የማቴዎስ ወንጌልን ከዚህ አይነቱና ሌሎች መጽሐፍት ቱውፊትን ካልተጠቀሙ እንዴት መለየት ቻሉ?
3. ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ላይ ፕሮቴስታንቶች በሚቀበሏቸው መልኩ 66ቱ መጽሐፍ ቅዱስ የተቀነነው(የተዘጋጀው) ከሉተር በኃላ ነው። ለአብነት ብንመለከት:-
=>>> ሶስቱ ሲኖዶሳውያት ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውኝን መጽሐፍት ይዘዋል።
1. 85 ሐዋርያውያት ቀኖናት 85ኛ ቀኖና ( Canons of the apostles)[1]:- ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን ከብሉይ ኪዳን መቃብያን መጽሐፍትን፣ ከሀዲስ ኪዳን መልእክታተ ቀለሜንጦስን አካቶ ይዟል። በአንጻሩ ደግሞ የዮሐንስ ራእይን አያካትትም።
2. ቀኖናት ዘሎዶቅያ/Council of Laodicea [2]:- የሎዶቅያ 60ኛ ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን መጽሐፈ ባሮክ እና ተረፈ ኤርሚያስን ይዟል በአንጻሩ ደግሞ የዮሐንስ ራእይን አያካትትም።
3. ቀኖናት ዘቅርጣግ (Codex Canonum ecclesiae africanae) [3] በመባል ይታወቃል። ይህ ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን መጽሐፈ ጥበብና የመቃብያን መጽሐፍትን ይዟል።
=>>>በቤተክርስቲያን አባቶች በግል ደረጃ የተቀነኑ ቀኖናዎች ስንመለከትም ዛሬ ላይ ፕሮቴስታንት እጅ ካለው የተለዩ ሆነው እናገኛቸዋለን። ለምሣሌ ቅዱስ አትናቴዎስ በ 367ዓ.ም በላከው የፋሲካ መልእክቱ 39ኛ ላይ የመጽሐፍትን ዝርዝር በቀኖና መልክ አስቀምጧል። [4]ቅዱስ አትናቴዎስ በዘረዘራቸው ውስጥ መጽሐፈ ባሮክና ተረፈ ኤርሚያስ(ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸው) ተካተው ሲገኙ መጽሐፈ አስቴር (ፕሮቴስታንቶች የሚቀበሉት) አልተካተተም።
=>>>እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ዛሬ 66ቱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው እውነተኛ፣ ሌሎች መጽሐፍት ሀሰተኞች/ተቀባይነት የሌላቸው የሚለው ሀሳብ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል? ከየትኛው ታሪካዊ የቀኖና ሂደትስ አገኙት?በእርግጥም ከጥንት የቤተክርስቲያን አባቶች ሉተር በልጦባቸው ይህን አድርገዋል።
=>>>በቀጣይ ጽሁፍ የሰማንያ አሃዱ መጽሐፍት ምንጮችን ለመመልከት እንሞክራለን።
ማጣቀሻ
[1]Michael D. Marlowe. "The "Apostolic Canons" (about A.D. 380)" . Bible Research . Archived from the original on 29 August 2010. Retrieved 2 September 2010.
[2] Council of Laodicea at bible-researcher.com . Retrieved 2011-10-05.
[4]የሰማንያ አሃዱ መጽሐፍት ምንጮች እና ቀኖናት-ዲበኩሉ ዘውዴ ገጽ 52
ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
©ዕቅበተ እምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
No photo description available.
19
1 Comment
23 Shares
Like
Comment
Share

 በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በእንተ ሰማንያ አሃዱ (ክፍል-2)
[የዲዩትሮካኖን/Deuterocanonical መጻሕፍት ምንጮች]
=>>>በኦርቶዶክስና በካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ በፕሮቴስታንቶች ዘንድ የማይገኙ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዲዩትሮካኖን(Deuterocanon) ተብለው ሲጠሩ ሁለተኛ የቀኖና መጻሕፍት ማለት ነው። በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ደግሞ ፕሮቶካኖን(Protocanon) ተብለው ሲጠሩ የመጀመሪያ ቀኖና መጻሕፍት ማለት ነው። ፕሮቶካኖን እና ዲዩትሮካኖን የሚለው ቃል ቅደም ተከተልን (Chronological Order) የሚያሳይ እንጂ በመጻሕፍቱ መካከል ለየቅል የደረጃ ልዩነት እንዳለ (Distinction in Status) የሚገልጽ አይደለም። [1] ይህም ማለት ዲዩትሮካኖኒካል የተባለቡት ዋናው መክንያት በቀኖና የተመዘገቡበትን የታሪክ ምእራፍ ለማመልከት ነው።
=>>>የመጀመሪያዎቹ የብሉይ ኪዳን ቀኖና መጻሕፍት(Protocanonical Books) በእስራኤል የመመለስ ዘመን ካህኑና ጸሀፊው ዕዝራ በሠራው ቤተ መጻሕፍት ውስጥ አስቀምጧቸዋል። በዚህ ወቅት የተሰበሰቡት መጻሕፍት በአይሁድ እጅ የተገኙት ብቻ ነበሩ። በሳምራውያን እና በኤሴያውያን እጅ የነበሩ መጻሕፍት በወቅቱ አልተሰበሰቡም። [2] በሁለተኛ መቃብያን እንደ ተጻፈው ነህምያ ቤተ መጻሕፍት ባቋቋመ ጊዜ የነገሥታትንና የነብያትን መጻሕፍት የዳዊት መዝሙራትና የነገሥታትን ደብዳቤዎች አሰባስቧል። ዕዝራና ነህምያ በሌሎች የአይሁድ ክፍሎች (ሳምራውያንና ኤሴያውያን) እጅ የነበሩትንና ከእነርሱ በኃላ የተጻፉትን መጽሐፍት አላሰባሰቧቸውም።
=>>>ሁለተኛዎቹ የብሉይ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍት (Deuterocanonical Books) ከእዝራና ከነህምያ በኃላ የተጻፉ ወይም ቀድመው ቢጻፉም በኃላ ተሰባስበው ወደ ቀኖና የገቡ መጻሕፍት ናቸው። እስራኤላውያን በግብጽ በባቢሎንና በፋርስ በተደጋጋሚ በደረሰባቸው ስደት የተነሳ መጽሐፍት ተበታትነው ይገኙ ነበር። በተለይም ከ 2ኛው ክ/ዘመን በኃላ ወደ ቁምራን ዋሻ (ሙት ባሕር አካባቢ) መሰባሰብ የጀመሩት ኤሴያውያን የያዙዋቸው መጻሕፍት ለብዙ ዘመናት ተጠብቀው ቆይተዋል። ከዚያ በኃላ የተነሱ የአይሁድም የክርስቲያንም ሊቃውንት እየተፈለጉ ሲገኙ ለቀኖና በመብቃታቸው ሁለተኛ የቀኖና መጻሕፍት ለመባል ችለዋል። [3]
=>>>የዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ምንጮች እና ቀኖናዊ ማረጋገጫዎች:-
፩. መጽሐፍ ቅዱስ:- የሀዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጸሀፊዎች ከዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት እየጠቀሱ ጽፈዋል። ይኸውም መጻሕፍቱ ተአማኒነት እንዳላቸው የሚያረጋግጥ ነው። ለአብነት የሚከተሉትን ጥቅሶች መመለከት ይቻላል።
1. ይሁዳ ጌታን በሠላሳ ብር ከሸጠው በኃላ ተጸጽቶ ሠላሳውን ብር ለካህናት አለቆች መልሶላቸዋል። እነርሱም የሸክላ ሠሪን መሬት ገዝተውበታል። ይህ አስቀድሞ በነብዩ ኤርሚያስ የተነገረ ትንቢት ነው። ይህ ትንቢት አስቀድሞ ከዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት አንዱ በሆነው በተረፈ ኤርያስ ተጽፏል።
"በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው። ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት። የሚል ተፈጸመ።" ማቴ27÷9-10
"የእስራኤል ልጆች የተስማሙበት የክርስቶስን ዋጋ ሠላሳውን ብር ይቀበሉታል። ያንንም ብር ለሸክላ ሠሪ ቦታ ዋጋ አድርገው ይሰጡታል" ተረፈ ኤርሚያስ 7÷3 (1980 እትም)
2. አይሁድ ጌታችንን መከራ እንዳደረሱበት፣ እንደ ዘለፉት እና ለሞት አሳልፈው እንደሰጡት በመጽሐፈ ጥበብ በትንቢት የተቀመጠውን እና በወንጌላት የተጻፈውን በማነጻጸር ማየት ይቻላል።
ትንቢት:- "የእግዚአብሔር እውነተኛ ልጅ እንደሆነ ያድነው ከሚቃወሙትም ሰዎች እጅ ያድነው" ጥበብ2÷18
ፍጻሜ:- " በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።"
ማቴ 27:43
ትንቢት:- "ቅንነቱን እናውቅ ዘንድ እየሰደብን በመከራ እንመርምረው እንደ ቃሉ ረዳት ይሆነው እንደሆነ የከፋ የተዋረደ ሞትን እንፍረድበት አሉ" ጥበብ2÷19-20
ፍጻሜ:- "ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤ ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።" ሉቃ22÷63-65
3. በወንጌል ላይ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመፈተን የቀረቡ ትንሳኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን እንደ ነበሩ ተጽፏል።
"ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት....ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች? ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። ከመጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።" ማቴ22÷24-28
ሰዱቃውያ ይህን ታሪክ ከመጽሐፈ ጦቢት ነው የወሰዱት። እነርሱ እሱን ለመፈተን ታሪኩን ቢጠቅሱትም መጻሕፍትን አታውቁምና ትስታላቹ ብሎ መልስ ሰጥቷቸዋል።
"እንሆ ሰባት ሰዎች አገቡሽ ባሎችሽ እየታነቁ እንዲሞቱ አታውቂምን? አሏት። ከነርሳቸው አንዱ እንኳን አልቀረሽም። እነርሳቸውም ሞተዋልና..." ጣቢት3÷8
4. ከጌታ ሐዋርያት ከሆኑት አንዱ ይሁዳ ሄኖክ ስለ ተናገረው ትንቢት ጽፏል። የሄኖክ ትንቢት በመጽሐፈ ሄኖክ ላይ ተጽፎ ይገኛል።
" ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ። እነሆ፥ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ... ሁሉ እንዲወቅስ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ።"
ይሁ 1:14-15
"ለወዳጆቹ ይፈርድላቸው ዘንድ እንሆ ከብዙ መላእክት ጋራ ይመጣል። ሕገ እግዚአብሔርንም የዘነጉ ሰዎች ያጠፋቸዋል።"
መጽሐፈ ሄኖክ 1÷9
5. ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ ከመጽሐፈ መቃብያን ጠቅሶ ጽፏል።
" ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።"
1ኛቆሮ 2:9
"ለደጋግ ሰዎች የተዘጋጀች ደስ የምታሰኝ ዓይን ያለየውን ጆሮም ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን እግዚአብሔር ደስ ላሰኙት ያዘጋጀውን..." 1ኛመቃ14÷20
6. ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱም ከመጽሐፈ መቃብያን ጠቅሶ አስተምሯል።
" ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤"
(ወደ ዕብራውያን 11:35)
ይህ ታሪክ በቀጥታ ከመጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ከምእራፍ 3 የተወሰደ ታሪክ ነው። 1ኛመቃ3÷1-38 ይመልከቱ።
7. በትንቢተ ኤርሚያስ ላይ የኤርሚያስ ደቀ መዝሙር የነበረው ባሮክ ጸሀፊ እንደ ነበር ተጽፏል። ደግሞም ከኤርሚያስ የሚሰማቸውን ነገሮች ይጽፍ እንደ ነበር ተጽፏል።
"ኤርሚያስም ሌላ ክርታስ ወሰደ ለኔርያም ልጅ ለጸሐፊው ለባሮክ ሰጠው እርሱም የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም በእሳት ያቃጠለውን የመጽሐፍ ቃል ሁሉ ከኤርሚያስ አፍ ጻፈበት ደግሞም እንደ ቀድሞ ያለ ቃል ብዙ ቃል ተጨመረበት" ኤር36÷32
ይህ ሀሳብ ለመጽሐፈ ባሮክ ፍንጭ የሚሰጥ ነው። ባሮክ ጸሀፊ ከነበረ ባሮክ የጻፋቸው መጽሐፍት ወዴት አሉ? የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል።
በቀጣይ ክፍል የዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ሌሎች ምንጮችን እንመለከታለን።
ማጣቀሻ
[1] Catholic Encyclopedia, Canonof the Old Testament
[2]The Bible through the Ages p-127
[3]Pope Shenouda lll CD, Coptic Orthodox Church, Australia, 1988
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
©ዕቅበተ እምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
No photo description available.
9
17 Shares
Like
Comment
Share