Wednesday 6 May 2020

አሁን ነበር እክቲቪስት መሆን...!!የተወደደው የፍልስፍና አስተማሪ ዮናስ ዘውዴ ከተናገራቸው አንኳር አንኳር ሃሳቦች ጥቂቱን እነሆ ብያለሁ ቅዱሳን መልካም የውይይት ጊዜ ነበረ ወንድማችንን ዘማሪ ፓስተር ኬፋን እግዚአብሔር ይባርከው ወንድማችን ዮናስ በዕድሜው ወጣት የሆነ ሰውና የሀገር ተስፋም ሆነ የቤተክርስቲያን ተስፋ የሚጣልበት እግዚአብሔር የሰጠን ወንድም ነው :: በጥልቀት ታስበው ፣ በውስጡም ተቀምጠው ያሉ ሃሳቦቹና ንግግሮቹ በእውቀት የዳበሩ ፣ ትውልድንም የሚገነቡ በመሆናቸው በማስተዋል ልንሰማው ልንማርበትም ይገባል ስል ሃሳቤን አክዬ ለመሰንዘር እወዳለሁ :: የክፍል ሁለት ውይይቱ ይቀጥላል አሁን ግን የክፍል አንድን ውይይት ተከታተሉ :: ከሰነዘራቸው ሃሳቦቹም መካከል ጥቂቶቹ እነዚህ ናቸው :: ወፍ እንደ ሀገርዋ ነው የምትጮኸው :: መሰልጠንና መሰይጠን ልዩነት አላቸው :: በነበረውና በአዲሱ ነገር መካከል ያለውን እንዴት እናስኪደው ግን እንደ ሀገር የሚያስፈልገን ሁሉን በሚዛን ሁሉን በልኬት ማየት መቻል አለብን :: መሠልጠን መከባበር ነው ብዬ ነው የማስበው :: መሪን በማዋረድ መተለቅ ይቻላል ብዬ አላስብም :: መሪን ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም ነገር ማለት ነው :: አንድ ሰው ስለነቀፈህ ብቻ የነቀፈህ ነቀፌታ ልክ ነው ማለት አይደለም :: ሰውየው ስላለው ልክ አይሆንም ፣ ሰውየው ስላላለውም አይደለም :: ነገሩ በራሱ ነው ኦብጀክቲቭሊ መታየት ያለበት ስለዚህ እነርሱን ብናደርግ ፣ የሰለጠነ አዕምሮ ባለቤቶች ብንሆን ፣ ስለ ሥልጣኔ ያለን አስተሳሰብም በልኬት ቢሆን :: መሠልጠን ፣ ማወቅ ማለት ከአሜሪካና ከአውሮፓ መምጣት ነው ብዬ አላስብም እኔ በማለት ሃሳቡን ሊያካፍለን ወዷል :: ጌታ እግዚአብሔር ዘመኑን ይባርከው

ለኪዳን ሕዝብ የተገባ ኑሮ ( ክፍል አንድ ) በአንድ ቤት ውስጥ የሁለት ኪዳን ኑሮ ( ገላትያ 4 ፥ 21 - 31 ...